Amhara FM Bahir Dar 96.9
96.90
Amharic
Genre: News-Talk
Station Description
የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ታሪክ የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ሢመሠረት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባሕል፣ ቱሪዝም እና ማስታወቂያ ቢሮ ውስጥ አንድ መምሪያ ኾኖ ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ የክልሉ የዜና ማዕከል ኾኖ ያገለግል ነበር፡፡ ድርጅቱ በ1986 ዓ.ም. የሰው ኃይሉ ቁጥር ከ13 አይበልጡም ነበር፡፡ የሥራ መሳሪዎቹም አገልግሎት የሰጡ፣ ፍጥነት እና ጥራታቸው እምብዛም የኾኑ እና ለሥራ አስቸጋሪ ነበሩ፡፡ በወቅቱ ጋዜጠኞቹም ቢኾኑ የተሰባሰቡት ከኢትዮጵያ ሬዲዮ፣ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተመርጠው የተውጣጡ ናቸው፡፡ በዚያን ጊዜም በድምፅ፣ በፎቶ፣ በጽሁፍ እና በተንቀሳቃሽ ምስል የተዘጋጁት ዘገባዎች በስልክ፣ በፖስታ ቤት፣ በአውሮፕላን ተልከው ለታዳሚያን ይደርሱ ነበር፡፡ ታሕሳስ 7 ቀን 1987 ዓ.ም. ስለአማራ ክልል በጋዜጣ መረጃ ለሚያገኙ የሕትመት ብርሃን የታየበት ቀን ነው፡፡ በወቅቱም “በኩር” የሚል ስያሜ የተሰጠው ጋዜጣ ተመስርቷል፡፡ የስያሜው ቃል ትርጓሜም የመጀመሪያ እንደማለት ነው፡፡ ስምንት ገጽ ያለውን ሳምንታዊ ጋዜጣ ለማተም ጋዜጠኞቹ ጽሁፍ እና ፎቶግራፎችን በሙጫ አጣብቀው፤ ወደ ማተሚያ ቤት በፖስታ ቤት አዲስ አበባ ልከው፤ እንደገና በአውቶብስ ተጭኖ ለዞን እና ወረዳ አንባቢያን ይደርስ እንደነበር ታሪካዊ ዳራው ይዘክራል፡፡ የህትመቱ ይዘቶችም ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ዜና እና ዜና ትንታኔ እንዲሁም አስተማሪ እና አዝናኝ መጣጥፎች ነበሩ፡፡
Loading ads...
Live Listener Chat
Log in to join the live chat.